Proverb
stringlengths 4
244
|
---|
ዳክዬን ከውሃው፤ ፈረስን ከገለባው። ዳዊት በሹክሹክታ፤ ሰአታት በጋጋታ። ዳዊት በገናውን፤ ዕዝራ መሰንቆውን። |
ዳዊትን ያህል መዝሙር፤ ጨለማን ያህል ጥቁር (የለም)። ዳዋ በበላ፤ ጎመን በደላ እንዱሉ። |
ዳገት ለወዳጁ አይሰንፍ፤ ሀብታም ካለ ወዳጅ አይተርፍ። ዳገት ሲወጡ ጥግ ጥጉን፤ ዳቦ ሲበሉ ልብ ልቡን። |
ዳገት ዕርሙ፤ ሜዳ ወንድሙ። ድል በመታደል፤ ሙያ በመጋደል። ድል እድል፤ በአንድ ድልድል። ድል፥ የባለ እድል። |
ድሀ ለወዳጁ አይሰንፍ፤ ሀብታም ካለወዳጁ አይተርፍ። |
ድሀ ማታ አሥር ይጠምዳል፤ ጧት አንድ ያጣል። (ማታ ~ በሕልሙ) ድሀ፥ ምን ትሠራለህ እንጂ፥ ምን ትበላለህ የሚለው የለም። |
ድሀ ሰው ድሮ ከአረደ፥ ከኹለት አንዳቸው ቢታመሙ ነው። ድሀ ሲቀልጥ፥ አመድ አመድ ይሸታል። |
ድሀ ሲቀልጥ፤ አመድ ይቀልጣል። |
ድሀ ሲቀመጥ፥ እጁን ይህ አወዚውው። |
ድሀ ሲቀማጠል፥ ከወገቡ ቀምጠል። (ቀምጠል ~ ቅምጥል) |
ድሀ ሲቆጣ ከንፈሩ ያብጣል፥ መንገደን ያሰልጣል። ድሀ ሲናገር ሬት ኮሶ፥ ሀብታም ሲናገር የማር በሶ። ድሀ ሲንቀባረር፥ ያለቀሰ ይመስላል። |
ድሀ ሲቆጣ፥ መንገድ ያፈጥነዋል። (መንገድ ያፈጥነዋል ~ እግሩ ይፈናጠራል) ድሀ ሲቆጣ፥ እግሩ መንገድ ያሰልጣል። |
ድሀ ሲያስለቅሱ፥ ከሥላሴ ይወቀሡ፥ መንግሥተ ሰማያትን አይወርሱ። ድሀ ሲያገኝ፥ ያጣ አይመስለውም። |
ድሀ ቅቤ ወድ፥ ማን ሉሸከም ነድ? |
ድሀ በሕልሙ ቅቤ ባይጠጣ ኖሮ፥ እከክ በወረሰው። (ኖሮ ~ ኑሮ) ድሀ በሕልሙ ቅቤ ባይጠጣ ኖሮ፥ እከክ ይጨርሰው ነበር። |
ድሀ በሕልሙ ቅቤ ባይጠጣ፥ እከክ በፈጀው። (እከክ ~ ንጣት) |
ድሀ በሕልሙ ቅቤ ባይጠጣ፥ እከክ ይጨርሰው ነበር። (ይጨርሰው ~ ይገድለው) |
ድሀ በሕልሙ፥ ቅቤ ባይጠጣ (ኖሮ)፥ ንጣት ይገለው ነበር። ድሀ በሕልሙ ቅቤ ባይጠጣ፥ ንጣት በገደለው። |
ድሀ በመሆኔ፥ ተባልኩኝ ቦኔ። |
ድሀ በሽታ አያውቅም፤ ሀብታም ጤና የለውም። ድሀ፥ በቤቱ ንጉሥ ነው። |
ድሀ በአመደ፤ ንጉሥ በመደ። ድሀ በጉልበቱ፤ ባለጸጋ በከብቱ። |
ድሀ ቢናገር አያደምቅ፤ ቢጨብጥ አያጠብቅ። |
ድሀ ቢያስለቅሱ፥ ከሥላሴ ይወቀሡ፥ መንግሥተ ሰማያትን አይወርሱ። ድሀ ባይ፤ አይኔን አመመኝ። |
ድሀ ተበድል ራሱ ይታረቃል፤ ሀብታም በድል ተመልሶ ይሥቃል። ድሀ አገር እንጂ፥ ቤት የለውም። |
ድሀ ተበድል፥ ማሩኝ ይላል ቶል። |
ድሀ እስኪለብስ፤ ሸንጎ ይበተናል። ድሀ ከንቡ፥ ይደላ። (ይዳላ ~ ይዳራ) ድሀ ከንቡ ይደላል። |
ድሀ ከአለቀሰ፥ ቀኑ መች አነሰ። |
ድሀ ከአልጣረ፥ ድሮ ከአልጫረ፥ ማን ያበላው ነበረ? ድሀ ከዕርሻ፥ ዳቦዬን ለማንሻ። |
ድሀ ከአልራ፤ ድሮ ከአልጫረ (ማን ያበላው ነበረ)? ድሀ ከአልጋረ፤ ድሮ ከአልጫረ። |
ድሀ ውሃውን ጠጥቶ እሳቱን ይሞቃል፤ ሀብታም ስለ ገንቡ ይጨነቃል። ድሀ የሚበላው እንጂ፥ የሚከፍለው አያጣም። |
ድሀ የሚበላው እንጂ፥ የሚከፍለው አያጣም። (የሚበላው ~ ይበላው ~ ይከፍለው) |
ድሀ ያልፍልኛል ይላል፤ ጌታ ቀኑን ይቆጥራል። ድሀ ያመልክት፤ ዳኛ ያሟግት። |
ድሀ ይበላው እንጂ፥ ይከፍለው አያጣም። ድሀ ይረጋ፤ ደረቅ ቆዳ ይጮህ። |
ድሀ ጉልበቱን፤ ባለጸጋ ከብቱን። |
ድሀና ሹም ተሟግቶ፤ ድንጋይና ቅል ተማትቶ። (የማይሆን ነው ከቶ) ድሀና እመቤት፤ እልፍኝና ማድቤት። |
ድሀና እጦት፤ አህያና አመድ (አይተጣጡም)። ድሀና ድመት፥ ሉሞት ሲል ያምርበታል። ድሀና ገበያ፥ ሳይገናኙ ይሞታል። |
ድሀና ጌታ ተሟግቶ፤ ድንጋይና ቅል ተማትቶ የማይሆን ነው ከቶ። ድሀና ጨራ፥ እየጮኸ ይበሎል። |
ድሀን ምን ትሠራለህ እንጂ፥ ምን ትበላለህ የሚለው የለም። |
ድሀን ቢያስለቅሱ፥ በሥላሴ ይወቀሡ፥ መንግሥተ ሰማያትን አይወርሱ። ድሀን ከአስለቀሱ፥ በሥላሴ ንድ ይወቀሡ። |
ድሀን ፈርቼ፥ ደጄን በቀን ግቼ። ድህነት፥ ከአምላክ መስማማት። ድህነት፥ ከአምላክ መስተካከል። |
ድል ድል፤ እድልህ እንዳይጎድል። ድልህን፥ በርበሬ አስመሰገነው። ድመት ላመሎ፥ ዚፍ ላይ ትወጣለች። |
ድመት መንኰሳ፥ መናከሷን አትረሳ። (መናከሷን ~ አመሎን) ድመት በታች ከሆነች፥ ታሸንፋለች ውሻን። |
ድመት፥ ውስጥ ውስጡን አውሬ ናት። ድመትና ቁንጫ፥ ባድ ቤት ይወዳል። ድመትና አይጥ፤ እሳትና ጭድ። ድመትን፥ በቆል መጠርጠር። |
ድመትን አይጥ ገደለቻት፥ ወይ ጥቃት ወይ ጥቃት። ድምፅና ቁንጫ፥ ባድ ቤት ይወዳል። |
ድምፁን የማያሰማ ባል። |
ድሪቶ ከነቅማሉ፤ መጥፎ ሰው ከነአመሉ ወዱያ በሉ። ድሪያ፥ የዝሙት ዋንጫ ዋዛማ። |
ድር ቢያብር፥ አንበሳ ያሥር። ድር ቢያብር፥ ጋቢ ይሠራል። ድርብርብ፥ እንደ ደጋ ንብ። ድርና ማግ፤ ለሀጭና ልጋግ። ድርጎ ራቱ፥ ድርጎ ቢቀር ሞቱ። |
ድርጎ የለመደች መበለት፤ ወተት ያየች ድመት። ድርጭት ፈንጠር፤ ምዝግዝግ ጎንደር። |
ድሮ ላትበላው፥ ታፈስ። |
ድሮ በልቶ ብስና፤ ጎመን በልቶ ጤና። ድሮ በልቶ ከብስና፥ ጎመን በልቶ በጤና። ድሮ በልጇ አንጀት ትጫወታለች። |
ድሮ በማሰሮ፤ ገደል ለዝንጀሮ። (ማሰሮ ለድሮ ገደል ለዝንጀሮ) ድሮ በጋን። |
ድሮ ቢያማት፥ በሬ ተሳሉላት። |
ድሮ ቢጠፋ ከቤቱ፥ መነኮሰች እናቱ። |
ድሮ ብታልም፥ ጥሬዋን። (ሕልም ብታይ ) ድሮ ብትታመም፥ በግ አረደላት። |
ድሮ ነበር እንጂ፥ መጥኖ መደቆስ፥ አዅን ምን ያደርጋል? ወጭት ጥድ ማልቀስ። |
ድሮ ከቆጥ፤ በሬ ከጋጥ። |
ድሮ ከቤት ውላ፥ ዝናብ ይመታታል። ድሮ ከተከተተ፤ ጅብ ከአኮተኮተ። ድሮ ከአልበሎት፥ አሞራ ናት። |
ድሮ ከአልጫረ፤ ድሀ ከአልራ። |
ድሮ ከአያታችን፥ ከአጤ ነው ትውልዳችን። |
ድሮ ከጋጥ፤ በሬ ከቆጥ። (በሬ ~ አህያ) |
ድሮ ከጮኸ ላሉት የለም፤ ከደብረ ታቦር ወዱያ ክረምት የለም። ድሮ ከጮኸ የለም ላሉት፥ ከቡሄ ወዱያ የለም ክረምት። |
ድሮ ከጮኸ ላሉት፤ ከደብረ ታቦር ወዱያ ክረምት የለም። |
ድሮ ካልጫረ፤ ድሀ ካልራ። |
ድሮ ጭራ መታረጃዋን፥ አወጣች ማረጃዋን። ድሮ:_ ጭራ የምታወጣው ምሥጢር። |
ደሮ ጭራ ጭራ፥ አወጣች ማረጃዋን ካራ። |
ደሮ ጭራ ጭራ፥ የራሷን አጥንት አወጣች። |
ድሮ:_ ጭራ ጭራ መታረጃዋን ታወጣለች። ድሮ ጭራ ጭራ፥ ታወጣለች ካራ። |
ድሮ፥ ሲሉ ሰምታ፥ ሞተች በጢስ ገብታ። (በጢስ~ ከጢስ ~ እጢስ ~ እጪስ) |
ድሮ፥ ቢጠፋት፥ ብታስገኝልኝ በቅል እስጥሀለኹ ባል ተሳለች። ድሮ፥ ባሎ ሲሞት፥ ሞተች እጢስ ገብታ። |
ድሮ፥ አንደን እንቁላል በወለደችበት፥ ወታቦ ትሞላለች። ድሮ እቤት ውላ፥ ዝናብ ትመታለች። |
ድሮ፥ እኔ ባልበላው፥ ጭሬ አላፈሰውም ወይ አለች። ድሮ ከቆጥ፤ ሴት ከማጀት። |
ድሮ(ን) ሲቀጣጥቧት፥ በመጫኛ ጣሎት። |
ድሮም ላባ ሲሰርቅ እንጂ፥ ሲካፈል አይስማማም። ድሮም እንዳይሆን ነው፥ የቄስ ልጅ መኮንን (አለ)። ድሮም የቂጥ ወሮታው፥ ፈስ ነው። |
ድሮና ቀበሮ፥ ተገናኝተው ሮ። (ተገናኝተው ~ ተገናኝቶ) ድሮና ሴት ከቤት ውላ፥ ዝናብ ትመታ። |
ድሮን ሲያታልሎት፥ በመጫኛ (ጠልፈው) ጣሎት። ድሮን ሲያታልሎት፥ አንቺ ሩጭ እኛ እንከተልሽ አሎት። ድሮን ሲያታልሎት፥ ጥምር መንግሥት አሎት። |
ድሮን ሲያታልሎት፥ ፎቶ አነሧት። ድሮ(ን) ሲደልሎት፥ በመጫኛ ጣሎት። ድክተር ሲበዚ፥ በሽተኛ ይሞታል። |
ድሮን ቢያማት፥ በሬ ተሳሉላት። |
ድስት ግጣሙን አያጣም። |
ድበላ፥ አንዳንድ ጊዛ ይበላ። ድንቀኛ ተሽ፥ ድር ይበጥሳል። |
ድንቁርና፥ ከልብህ መካከል፥ ተራራ ያህል። ድንቢጥ እንደ አቅሟ በብዕር ትታገማለች። ድንቢጥ እንዳቅሟ፥ በብርዕ ትታገም። ድንን ተገልጦ፤ ዙፋን ረግጦ። |
ድንጋይ ለረገጠ ፍለጋ የለውም፤ ውሃ ለጠጣ ሽታ የለውም። ድንጋይ ላይ ተቀማጭ፥ የባለጌ ተለጣጭ። |
ድንጋይ ሲያረጅ፥ መጭ ያበቅላል። |
ድንጋይ በድንጋይ ላይ ትልቅ ቤት ይሆናል። ድንጋይ ቢቆሉት፥ አይሆንም ቆል። |
ድንጋይ ቢያጎኗት፥ ተመልሳ ከአናት። ድንጋይ ትራሱ፥ ዳዋ ልብሱ፥ ኮቾሮ ጉርሡ። ድንጋይ እና ቅል አይፈናከቱም። |
ድንጋይ ወርድ እብጥ ያርፋል፥ ያገኘው ይተርፋል። |
ድንጋይ ወርድ ከብጥ ያርፋል፥ ሰው በሞቱ ወደ መቃብር ያልፋል። |
ድንጋይ ወደ ሰማይ ቢወረወር፥ ተመልሶ (ወደ) ምድር። |
ድንጋይ ውሃ ውስጥ ስለኖረ ዋና አይለምድም። |
ድንግል አልቅሳ፥ አወጣች አንድ አበባ፥ ያን አበባ፥ አስረው ገረፉት እንደ ላባ። |
ድንቢን ያየ ባለጌ። |
ድንቢን ገልጦ፤ ዙፋን(ን) አጊጦ። (አጊጦ ~ አግጦ ~ ረግጦ) ድንገተኛ ስሕተት፤ የቁልቁለት ውድቀት። |
ድከሚ ያላት ጥቁር ሴት፥ እጇን ትነቀሳለች። ድሀ ኹለት፤ ድንበር አለው። |
ድክተሮች ሲበዙ፥ በሽተኛው ይሞታል። |
ድግስ የላለው ዋዛማ፥ ምልክት የላለው ዛማ። ድግርና ገባር፥ ሲተካከል ያምር። |
ድጥ ማንሸራተቱን፤ ባለጌ ማሽሟጠጡን አይተውም። ድማ ለመማሻ፤ ማረሻ ለመፈለሻ። |
ጀማሪ ይጥፋ፤ ሰካራም ይትፋ። |
ጀምሮ የማይፈጽም፤ ፈጭቶ የማያልም። |
ጀምሮ ይጨርሳል፤ ለጉሞ ይተኩሳል አልሞ። |
ጀርባ ለባለቤቱ ባዕድ ነው። |
ጀርባ ጀርባው ይታያል። ጀርባው ከብድታል። |