Proverb
stringlengths 4
244
|
---|
ለኀጥአን የወረደ መዓት፥ ለጻድቃን ይተርፋል። ለኀጥአን የወረደ፥ ለጻድቃን ይተርፋል። ለዅሉም ጊዛ አለው። |
ለነገረኛ መንገድ፤ ለሆዳም ገበታ ይተዋል። ለነገረኛ ሰው፥ ጀርባህን ስጠው። |
ለነገረኛ ነገር ተውለት፤ ለሆዳም እህል አቅርብለት። ለነገር ዋነኛ፤ ለጦር አርበኛ። |
ለነፍስህ፥ ገዳም አለልህ። |
ለንጉሥ የማይረዳ፤ ከባሕር የማይቀዳ። ለንጉሥ የማይገዚ፥ ለእግዙአብሔር(ም) አይገዚ። |
ለንጉሥ የቀነቀነ ወርቅ፤ ለእግዛር የቀነቀነ ጽድቅ። |
ለንጉሥ ያልረዳ፤ ከባሕር የማይቀዳ። (የማይቀዳ ~ ያልቀዳ) ለንፉግ ሰው፥ የገበያ መንገድ ይጠበዋል። (ይጠበዋል ~ ይጠበው) ለአህያ ማር አይጥመውም። |
ለአህያ ማር አይጥመው፤ ለደንቆሮ ምክር አይገባው። ለአህያ ማር አይጥማት፤ ለሴት ምክር አይገባት። ለአህያ ማር አይጥማት(ም)። |
ለአህያ ያልከበደው፥ ለመጫኛ ከበደው። ለአህያ ፈስ፥ አፍንጫ አይዙለትም። ለአለው፥ ቅንጭብ ያረግዳል። |
ለአለው ይሰጡታልም፥ ይጨምሩለታልም። ለአለው ይጨመርለታል። |
ለአለፈ ነገር፥ ቤት አይሠራለትም። |
ለአለፈ(ው) አይጸጸቱም፤ ለሚመጣው አይበለጡም። |
ለአለፈ(ው) ክረምት፥ ቤት አይሠራለትም። (አይሠራለትም ~ አይሠራም) ለአለፈው ክረምት፥ ውሃ ማቆር አይቻልም። |
ለአለፈው ጸልት፥ ከንቱ ጩኸት። ለአሉ ያሉት፥ ለአለዊ ሆነለት። ለአላወቀ(ው) ፎገራ ደር ነው። ለአላየ ልጅ፥ ዳቦ ፍሪዳው። |
ለአላየው የሚያስገርም፤ ለሰማው የሚያስደንቅ። ለአላዩ ልጅ፥ ዳቦ ፍሪዳው። |
ለአሣር የጣፈው፥ ቢነግድ አይተርፈው። ለአሽከር አደግ፥ ጌታ አትደር። |
ለአበባ የለው ገለባ፤ ለወሬ የለው ፍሬ። ለአባይ ልጅ፥ ውሃ ነሡት። |
ለአበባ፥ የለው ገለባ። |
ለአቤቱታ፥ የለው ይሉኝታ። |
ለአንበሳ አታበድር፥ ከአበደርክ አትጠይቅ። |
ለአንበሳ አይመትሩ፤ ለብልኅ አይመክሩም። (አይመክሩም ~ አይነግሩም) ለአንበሳ አይመትሩ፤ ለአዋቂ አይነግሩ። (አይነግሩ ~ አይናገሩ) |
ለአንተ መምከር፥ ጥቁር ድንጋይ ላይ፥ ውሃ ማፍሰስ ነው። ለአንተ የተባለ እንጀራ ላላ አያገኘውም፥ ሻግቶ ይቀራል እንጂ። ለአንተ ያለውን እንጀራ ይሻግታል እንጂ፥ ማንም አይበላውም። ለአንቺ ቁምነገርሽ፥ በሶብላ ወጥሽ። |
ለአንቺ ብርቅሽ፥ በሶብላ ወጥሽ። ለአንቺ ብርቅሽ፥ የንጋዳ ሙቅሽ። |
ለአንደ የነበለት፥ ለላላው ሳያካፋ አይቀርም። ለአንድ ብርቱ፥ ኹለት መድኀኒቱ። |
ለአንድ አልሚ፥ ጠኝ ቋሚ። (አልሚ ~ አራሚ) ለአንድ ያሉት፥ ለኹለት ይተርፋል። |
ለአንድ ጭቃ አገር፥ ጠኝ ምስለኔ። ለአኩራፊ፥ ምሳው ራት ይሆነዋል። ለአወቀባት፥ ገረገራም ዋልድባ ናት። ለአዋቂ ምክር፤ ላላዋቂ በትር። |
ለአዋቂ አትወቅበት፤ ለረጅም አትከንዳበት። ለአዋቂ አይነግሩ፤ ለአንበሳ አይመትሩ። ለአዋጅ ነጋሪት፤ ለጥጥ ልቃቂት። |
ለአያቱ ዕዳ፤ ለአማቱ ፍሪዳ። ለአይነ ስውር መስተዋት። ለአይን አምላክ አለው። |
ለአይን የሚከፋ፤ ለአፍንጫ የሚከረፋ። (የሚከረፋ ~ ይከረፋ) ለአይንና ለወዳጅ ጥቂት ይበቃል። (ይበቃል ~ ይበቃዋል) ለአገልጋይ ትዕግሥት፤ ለባለቤት መጠቃት። |
ለአገሩ ባዳ፤ ለሰው እንግዳ። ለአገሩ እንግዳ፤ ለሰው ባዳ። |
ለአገሩ ፊደል እንግዳ፤ ለአባቱ ቋንቋ ባዳ። ለአገሬ ሰው እንን ነጋሪት፥ አታሞ አይሰጠው። ለአጠፋ ምሕረት፤ ለአጣ ቸርነት። |
ለአፈ ግም፤ አፍንጫ ድፍን ያዝለታል። |
ለአፈኛ ሰው መመለስ፤ ለትኋን ልም ማጉረሥ። ለአፈኛ ሰው፥ ገደልም ሜዳ ነው። |
ለአፉ ለከት የለውም። ለአፍ ዳገት የለውም። |
ለአፍ ግም፤ አፍንጫ ድፍን ያዝለታል። ለአፍላ፥ የለው ጎፍላ። |
ለአፍታ የለውም ፋታ። |
ለእርድ የቀረበ በሬ፥ ቢላዋ አይፈራም። ለእሮሮ ሳይሆን፥ ለአመክሮ። |
ለእሳት ዕንጨት፥ ካልነሡት አይጠፋም። (ካልነሡት ~ ካልነፈጉት) ለእሳት ውሃ፤ ለጠጉር ቡሀ። |
ለእሳት ፍላት፤ ለጮማ ሥባት። |
ለእበጥ ፍላት፤ ለዕንጨት እሳት። ለእባብ እግር የለው፤ ለባዳ ውል የለው። |
ለእብለት ሥር የለው(ም)፤ ለእባብ እግር የለው(ም)። ለእብድም ቢሆን ባል አይጠፋም። (ባል ~ ሚስት) ለእኔ ቆንጆ፥ ለሰው ግን አይጥ። |
ለእኔ እናት ምን በጃት? ( ተሻላት ~ ረባት) |
ለእኔ እናት ምን ደላት? ያም አፈር ያም ድንጋይ ጫነባት። ለእንቁጣጣሽ ያልሆነ፥ ቀሚስ ይበጣጠስ። |
ለእኔ፥ ነግ በእኔ። |
ለእዙህ ሆዳ፥ ጠላኝ መዳ። ለእጅ ርቆ፤ ለአይን ጠልቆ። |
ለእግሩ የተጸየፈ፤ ለቂጡ አስተረፈ። ለእግር የተጸየፈ፤ ለራሱ አተረፈ። ለእግር የፈሩት፤ ለቂጥ ይተርፋል። |
ለእግዙአብሔር የቀነቀነ ለጽድቅ፤ ለጌታ የቀነቀነ ለወርቅ። ለእግዛር የተቀናቀነ ጽድቅ፤ ለንጉሥ የተቀናቀነ ወርቅ። ለከለላ ጥላ፤ ቢርብህ ብላ። |
ለከርሞ የሚያብድ፥ ንድሮ ሱሪውን ከፍ ከፍ ያደርጋል። ለከርሞ ድሮ፤ እንቁላል ለንድሮ። |
ለከሳሽ የለው መላሽ። |
ለካህን ጥምቀት፤ ለገበሬ ግንቦት። ለክፉ ያሉት፥ ለበጎ ይበጃል። ለክፋት ያደለው፤ አሳዳጊ የበደለው። ለኮ መሳቢያ፤ ወፍጮ ማላሚያ። ለወሬ ሞትዅ። |
ለዅሉም አጥንት፥ የለው መቅን። ለኺያጅ፥ የለውም ወዳጅ። ለሕልም ምሳላ የለውም። |
ለወሬ ሞትኩ፤ ለእህል (ተ)ሰለፍኩ። ለወሬ ወዳጁ ወሬ፤ ለመነኰሴ ጥሬ። ለወሬ የለው ፍሬ። |
ለወሬ የለው ፍሬ፤ ለአበባ የለው ገለባ። |
ለወሬ የቸኮለ፥ እናቱን በመንገድ (ላይ) ይረዳል። ለወርቅ ያሉት አንገት ላሽክት። |
ለወቀጣ አንድም ሰው አልመጣ፤ ለመጠጡ ከየጎሬው ወጡ። ለወታደር፥ ሰፊ መንደር። |
ለወታደር ሰፊ መንደር፤ ለወዱላ መልካም ደላ። ለወይሮ፥ መልካም ድሮ። |
ለወደላ፥ መልካም ደላ። |
ለወደደት:_ ሰው ልብ ደንገጥ፥ ሹሩባም ርገፍ ይላል። ለወዱላ፥ መልካም ደላ። |
ለወዳጁ የሚፈተፍት፤ ለጠላቱ የሚመክት። ለወዳጅ የማር ወለላ፤ ለጠላት አሜኬላ። ለወዳጅ ጠላት፥ አለመተኛት። |
ለወዳጁ:_ እሳት ይዞል በእጁ። |
ለወዳጅና ለአይን፤ ትንሽ ይበቃዋል። ለወገን ጽናት፤ ለጠላት ቅናት። |
ለወጡ ዕኑለት፤ ከእንጀራውም ጉረሡለት። ለወጡ ጊዛስ፥ ከደረቁም ጉረሡለት። |
ለወጡም ዕኑለት፥ አንዳንድ ጊዛ ደረቅ ጉረሡለት። ለወጡም ዕኑለት፤ ከእንጀራውም ጉረሡለት። ለወጡም ዕኑለት፤ ከደረቁም ብሉለት። |
ለወጥ የሚሻል፥ ቅልውጥ። |
ለዋስ አፍ የለው፤ ለጉንዳን ደም የለው። ለዋንጫ ቡሽ፤ ለውሃ ጉሽ የለውም። ለውሻ ምሳ የለው፥ ራት ብቻ። |
ለውሻ ሞት፥ ፊት አይነጩለትም። |
ለውሻዬ ያልኹትን፥ ልጄ ቢበላብኝ አልወድም። |
ለውሽማ ሞት፥ ፊት አይነጩለት(ም)። (አይነጩለት(ም) ~ አይነጭለት(ም)) ለውጡኝ ባይ፥ የሚሻለውን አውቆ። |
ለዓመት ልብስ፤ ለዕለት ጉርሥ። ለአማርኛ ግእዝ (ነው) ዳኛ። ለአምላክ ልንገረው፥ ለማያስቀረው። ለአምጪ(ው) ይግደደው። |
ለዕውር ዝማሜ፤ ለመላጣ ጋሜ (አይስማማውም)። ለእውነት ማማ፤ ለውሸት ጨለማ። |
ለዝናብ ጌታ፥ ውሃ ነሡ(ት)። |
ለዝንብ፥ ከትላንት ወዱያም ድሮ ነው። ለይቶ እንደፈፋ፤ አንል እንዳረፋ። |
ለይቶት፥ አባ ንጉሧ። ለደኅና ሰው፥ ዋጋ አነሰው። |
ለደኅና ሰው ውሸት፤ ለጅብ እሸት። ለደረቅ የመጣ እሳት፥ ርጥብን ያነዳል። ለደብተራ፥ መቋሚያና ጭራ። |
ለደደብ ማስረዳት፥ ድንጋይ ቅቤ መቀባት። ለደግ ንጉሥ፥ ዕለት ዕለት ማልቀስ። ለዱያብልስ ፀሩ መታገስ፤ ለረኃብ ፀሩ ማረስ። ለዳርቻው ሲሣሡ፥ መካከሉን ተነሡ። ለዳርቻው ሲሣሡ፥ ከነመሀሉም ተነሡ። ለዳርቻው የሣሡ፥ መሀሉን ተነሡ። |
ለዳባ ለባሽ፥ ነገርህን አታበላሽ። ለዳኛ አመልክት፥ እንዱሆን መሠረት። ለዳኛ የነገሩት፤ በርጥብ ያቃጠሉት። ለዳኛ ዳኛ፤ ለአንበሳ ተኩላ አለው። ለድሀ፥ ማን ሰጠው ውሃ። |
ለድሪ ያሉት አንገት፥ ለአሽክት። ለድንገቱ፥ ከእግሬ ስንድድ አለበቱ። ለድንጋይ፥ የለው አይን። |
ለድሮ አጥንት፥ መጥረቢያ አያስፈልገውም። |
ለድካም የጣፈኝ፥ ብነግድ አይተርፈኝ። ለድሮ ሲነግሩ፥ ምጥማጥ ይሰማል። |
ለድህነት የፈጠረው፥ ቢነግድ አያተርፍም። (አያተርፍም ~ አይተርፈው) ለድሪ ያሉት አንገት፥ ለአሸንክታብ። |
ለጅል ከመንገር፥ የአንድ ቀን ጎዳና መኼድ ይሻላል። ለጅብ፥ አንጀትን ልም አያደርጉም። |
ለጅብም፥ እንዳንተ ያለ ወንድም አለው። ለጆሮ አጥር የለውም። |
ለጆሮ ጥርስ፤ ለሆዳም ሥሥ። ለገላጋይ ደም የለውም። ለገበሬ፥ መልካም በሬ። ለገቢህ ተንገብገብ። |
ለገና ጨዋታ፥ አይቆጡም ጌታ። ለገደለ ጎፈሬ፤ ላረጋገጠ ወሬ። ለገዳም የረዳ፥ አይጎዳ። |
ለጉንዳን ደም የለው፤ ለዝንብ ቤት የለው። ለጉንፋን ምሱ፥ ገንፎ በትኩሱ። |
ለጋስ ቢለግስ፥ አበደረ እንጂ (እንዱያው) አልሰጠም። ለጌታ የነገሩት፤ በሠኔ የተከሉት አይጠፋም። |
ለጌታም ጌታ አለው። |
ለጎበዝ ሰንጋ ፈረስ፤ ለፈሪ ፍርፋሪ። ለጎበዝ፥ ስጠው ሰንጋ ፈረስ። |
ለጠጪ ሰው፥ የመጠጥ ወሬ አውራው። ለጣይም ፈንጋይ ያዝለታል። |
ለጥልና ለዳኛ ያለው ገንብ፥ አፋፍ ይቆያል። |
ለጥምቀት እታጭ ያለች ሙሽራ፥ መስክ አደረች ለከተራ። |
ለጥምቀት እንሶስላ ያልሞቀች ኮረዳ፤ በእንተ ማርያም የሚል የቆል ተማሪ ሳይዝ አቁማዳ። |
ለጥምቀት ያልሣሡት እንግጣ፥ በወሩ ሙሽራ ያመጣ። (እንግጣ ~ እስክስታ) ለጥምቀት ያልታጨ፤ በሠኔ ያልተላጨ። |
ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ። ለጥምቀት ያልሆነ ዝማሬ፤ ለሠኔ ያልሆነ በሬ። |
ለጥርጣሬ ምንጣሬ። |
ለጥቅም ሲታጠቁ፥ ከጎን ይጠንቀቁ። (ከጎን ~ ጎንዎን) ለጥፋት የታች ከተማ፥ ነጋሪት ቢጎሰም አትሰማ። ለጦም ግድፈት፤ ለበዓል ሽረት። |
ለጨለማ ጊዛ መብራት፤ ለመከራ ጊዛ ብልኀት። |
ለጨቅጫቃ ሰው ከማበደር፥ ይሻላል በእጄ ማደር። (በእጄ ማደር ~ በእጅ ማሳደር) |
ለጨዋ ልጅ ሸማህን፤ ለባለጌ በቅልህን አታውስ። ለጭሰኛ መሬት፤ ለሣር ቤት ክብሪት። |
ለጾም ግድፈት፤ ለባል ሽረት። ለፈረስህ አንገት፤ ለጋሻህ ዕንብርት። ለፈሪ ምድር አይበቃውም። |