[ { "question": "ከሚከተሉት መካከል የስራ ደብዳቤ ውስጥ ብቻ የሚገኝ የቱ ነው?", "a": "ቁጥር", "b": "ቀን", "c": "መግቢያ", "d": "ሐተታ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ከአጋም የተጠጋች ቁልቋል ዘላለም--------------------፡፡", "a": "ስታነባ ትኖራለች", "b": "ስትቀጥፍ ትኖራለች፡፡", "c": "ስታብብ ትኖራለች", "d": "አጋም አጋም ትሸታለች፡፡", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ከኳስ ጨዋታ ውስጥ ጨዋታው ሲደራ፣ \nአይቀርም መድረሱ ፈጽሞ ግፍተራ፡፡ የዚህ ቅኔ ወርቅ የቱ ነው?", "a": "ግፍተራ የሚባል ቦታ መጠራቱ አይቀርም፡፡ ", "b": "መገፋፋት አይቀርም፡፡", "c": "መገፋፋት በፍጹም መኖር የለበትም፡፡", "d": "ግፍ የሰራ ሰው ተራው መድረሱ አይቀርም፡", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "መልዕክትን ለመቀበያነት የምንጠቀምባቸው የክሂል ዓይነቶች የትኞች ናቸው?", "a": "ማዳመጥናማንበብ", "b": "ማዳመጥና መናገር", "c": "መጻፍና ማንበብ", "d": "ማንበብናመጻፍ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ከሚከተሉት መካከል ምዕላድ የሆነው የቱ ነው?", "a": "ሰው", "b": "ሰውነት", "c": "ሰዎች", "d": "ሰዋዊ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ልጁ እንደእስስት ባህሪው ይቀያየራል፡፡ በሚለው አገላለፅ ውስጥ ለልጁና ለእስስት የጋራ የሆነው ባህሪይ የቱ ነው?", "a": "ተቀያያሪነት", "b": "እስስትነት", "c": "ልጅነት", "d": "ተንኮለኝነት", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ከሚከተሉት ዐረፍተነገሮች አንዱ ትክክለኛ ሃሳብ አልያዘም፡፡", "a": "እንስሳት ቋንቋ ስለሌላቸው በደመነፍስ አይግባቡም ፡፡", "b": "ቋንቋ ለሰው ልጆች ብቻ የተሰጠ ጸጋ ነው፡፡", "c": "ንግግር በድምጸ አልባ እንቅስቃሴ ይደገፋል፡፡", "d": "የቋንቋ ክሂሎች አራት ናቸው፡፡", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ለተሾመ ይመሰከርለታል፤ለተሻረ ይመሰከርበታል ብንል የተሰመረባቸው ቃላት ምንን ይገልጻሉ፡፡", "a": "ተሿሚው አካል ሲጠቀም ፣ከሹመት የወረደው ይጎዳል ማለት ነው፡፡", "b": "ተሿሚው አካል ተጠቃሚ ፣ከሹመት የወረደው ጥቅም ፈላጊ መሆናቸውን ይገልጻል፡፡ ", "c": "ተሿሚው አካል ተጠቃሚ ፣ከሹመት የወረደው ጠቃሚ ነው ማለት ነው፡፡", "d": "ተሿሚው አካል ጠቃሚ ፣ ከሹመት የወረደው ተጠቃሚ ነው ማለት ነው፡፡", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "የጽሁፉ ርዕስ ምን ሊሆን ይችላል፡፡", "a": "ተፈጥሯዊ ፍላጎትና ስነስርዓት", "b": "የአስተሳሰብ ለውጥ", "c": "የተፈጥሮ ስጦታ", "d": "", "answerKey": "a", "context": "ምንባብ:\nሰው በተፈጥሮው የረሃብና የጥም ፣የበቀልና የመሳሰለው ፍልጎቱ ሁሉ እንዲፈጸምለት ይፈልጋል፤ነገርግን ማህበሩ እያንዳንዱ ሰው የተፈጥሮ ፍላጎቱን ለመፈጸም ሲል ሌሎቹን ሰዎች እንዳይጎዳ የሚወስንበት የጽህፈትና የልማድ ሕግ ሠራ፡፡ስለዚህ የተፈጥሮ ፍልጎቱን ለመፈጸም የማህበበሩን የጽህፈትና የልማድ ሕግ የተላለፈ ነውረኛ ተብሎ ይፈረድበታል፡፡\nአንድ ሰው ከሌላው የሚያስቆጣ ነገር ቢደርስበትና ለቁጣው ምክንያት የሆነውን ሰው ለማጥፋት ቢወድ፣ በማህበሩ ህግ ቅጣት እንደሚያስከትል ስለሚያውቅ ቁጣውን ለማብረድ ፣ሌላ የሚበቀልበት አማራጭ መንገድ መመፈለግ አለበት፡፡ስለዚህ የሰው ሰውነት የነጻነትና የጭቆና ውጤት ነው ማለት ይቻላል፡፡ይህ ነጻነትና ጭቆና ማህበሩ በረጅም ዘመን ዕድሜው ከልማዱ፣ከወጉ፣ከህጉ አዋህዶና አስማምቶ የሰራው ነው፡፡ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው ተወልዶ ውስጡ ሲገባ በሱ ተመርቶ መኖር አለበት፤ከማህበሩ ስርዓት አንድ ነቁጥ እንኳን አይተላለፍም፡፡\nበጠቅላላው የማህበር ትምህርት እያንዳንዱ ሰው ሲወለድ ይዟቸው የሚወለደውን ጠቃሚ ውጥኖች ነጻነት በመስጠትና በልዩልዩ መንገድ በመርዳት ጎጂዎቹነንም እንዲሁ በልዩልዩ መንገድ በመጠቆምና በማረም ሰውዬውን ማህበራዊ እንዲሆን ያደርገዋል", "grade": 10, "preamble": "ከዚህ በታች የቀረበውን ምንባብ መሰረት አድርጋችሁ ለሚከተለው ጥያቄ ከተሰጡት አማራጮች መካከል ትክክለኛውን መልስ ምረጡ፡፡", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ከሚከተሉት መካከል የምክንያትና ውጤት ትስስር የሌለው ሃሳብ የቱ ነው?", "a": "ቋንቋ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ አደጋ ተናጋሪ ሲያጣ እሱም አብሮ ይጠፋል፡፡", "b": "በርትቶ የሚያጠና ተማሪ ተገቢውን እውቀት ይቀስማል፡፡", "c": "የሰው ልጅ ቋንቋ ና የእንስሳት አንድነትም ልዩነትም አላቸው፡፡", "d": "ለስኬት ጥረት ወሳኝነት አለው፡፡", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ጭራሽ ሰነፍ የሆነን ሰው መግለፅ ብንፈልግ የትኛውን ፈሊጣዊ አነጋገር መጠቀም እንችላለን?", "a": "እጅ አደር", "b": "እጀ ሰባራ", "c": "እጅ አጠረው", "d": "አጀ አመድ አፋሽ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ጥርሱን ነከሰ ለሚለው ፈሊጥ ተመሳሳይ የሚሆነው የትኛው ነው?", "a": "ዛተ", "b": "ጥርሱን አደማ", "c": "ደፈረ", "d": "ተተናኮለ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ሞክሼ ፊደላት ___ ድምፅ አላቸው፡፡", "a": "ተመሳሳይ", "b": "የተለያየ", "c": "ሁለቱም መልስ ይሆናሉ", "d": "", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 1, "preamble": "", "category": "Grammar" }, { "question": "‹‹ልጅ የጫረው እሳት ለጎረቤት ይተርፋል›› ቢባል ምሳሌያዊ አነጋገሩ የያዘው ትርጉም ከሚከተሉት የትኛው ነው?", "a": "በልጅ የመጣ ጠብ ቶሎ አይበርድም፡፡", "b": "ልጅ ያለ ልጅ ጨመረ፡፡", "c": "የመልካም ልጅ ጎረቤት በብርድ አይጠቃም፡፡", "d": "ታታሪ ልጅ ለጎረቤቱ በረከት ነው፡፡", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ነገረ ውሽልሽል ማለት -------------- ማለት ነው፡፡", "a": "ቁምነገር የሌለበት", "b": "በደንብ የተሰራ ", "c": "ቁምነገረኛ", "d": "መናኛ ስራ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ትምህርትቤት ከገባን በኋላ የምንናገኛቸው የክሂል ዓይነቶች ከሚከተሉት የትኞቹ ናቸው?", "a": "ማንበብና መጻፍ", "b": "መናገርና መጻፍ", "c": "መጻፍና ማዳመጥ", "d": "ማዳመጥና መናገር", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "በማህበሩ ህግ መሰረት ነውረኛ የሚል ስያሜ የሚሰጠው የትኛው ክፍል ነው?", "a": "የማህበሩን ስርዓት የጣሰ ", "b": "የማህበሩን ስርዓት ያስተዳደረ ", "c": "የማህበሩን ስርዓት በእኩል ዐይን ያልተመለከተ", "d": "የማህበሩን ስርዓት ያከበረ", "answerKey": "a", "context": "ምንባብ:\nሰው በተፈጥሮው የረሃብና የጥም ፣የበቀልና የመሳሰለው ፍልጎቱ ሁሉ እንዲፈጸምለት ይፈልጋል፤ነገርግን ማህበሩ እያንዳንዱ ሰው የተፈጥሮ ፍላጎቱን ለመፈጸም ሲል ሌሎቹን ሰዎች እንዳይጎዳ የሚወስንበት የጽህፈትና የልማድ ሕግ ሠራ፡፡ስለዚህ የተፈጥሮ ፍልጎቱን ለመፈጸም የማህበበሩን የጽህፈትና የልማድ ሕግ የተላለፈ ነውረኛ ተብሎ ይፈረድበታል፡፡\nአንድ ሰው ከሌላው የሚያስቆጣ ነገር ቢደርስበትና ለቁጣው ምክንያት የሆነውን ሰው ለማጥፋት ቢወድ፣ በማህበሩ ህግ ቅጣት እንደሚያስከትል ስለሚያውቅ ቁጣውን ለማብረድ ፣ሌላ የሚበቀልበት አማራጭ መንገድ መመፈለግ አለበት፡፡ስለዚህ የሰው ሰውነት የነጻነትና የጭቆና ውጤት ነው ማለት ይቻላል፡፡ይህ ነጻነትና ጭቆና ማህበሩ በረጅም ዘመን ዕድሜው ከልማዱ፣ከወጉ፣ከህጉ አዋህዶና አስማምቶ የሰራው ነው፡፡ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው ተወልዶ ውስጡ ሲገባ በሱ ተመርቶ መኖር አለበት፤ከማህበሩ ስርዓት አንድ ነቁጥ እንኳን አይተላለፍም፡፡\nበጠቅላላው የማህበር ትምህርት እያንዳንዱ ሰው ሲወለድ ይዟቸው የሚወለደውን ጠቃሚ ውጥኖች ነጻነት በመስጠትና በልዩልዩ መንገድ በመርዳት ጎጂዎቹነንም እንዲሁ በልዩልዩ መንገድ በመጠቆምና በማረም ሰውዬውን ማህበራዊ እንዲሆን ያደርገዋል", "grade": 10, "preamble": "ከዚህ በታች የቀረበውን ምንባብ መሰረት አድርጋችሁ ለሚከተለው ጥያቄ ከተሰጡት አማራጮች መካከል ትክክለኛውን መልስ ምረጡ፡፡", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "መጨነቅ መጠበብ ለጠጅ ብቻ ነው፣\nለጠላ መድሐኒት ተወት ማድረግ ነው፡፡ የዚህ ቅኔ ህብረቃል ምን የሚለው ነው?", "a": "መድሐኒት", "b": "ተወት ማድረግ ነው፡፡", "c": "ለጠላ", "d": "ለጠጅ ብቻ ነው፡፡", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "‹‹ካልታረደ አይታይስባቱ ካልተናገረ አይታወቅ ብልሃቱ›› የሚለው ምሳሌያዊ አባባል ምንን ይገልጻል፡፡", "a": "የንግግርን ትልቅነት", "b": "የማዳመጥና የመስማትን", "c": "የማንበብን ትልቅነት", "d": "የመጻፍን አግባብነት", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ከተከለከለው ከጨፌ እየዋለች፣\nአልታለብ ብላ ያቺስ ላም እምቢ አለች፡፡የዚህ ቅኔ ወርቅ ከሚከተሉት የትኛው ነው?", "a": "እስላሟ ሃይማኖቷን ጣለች፡፡", "b": "ላሚቱ አልታለብ አለቸ፡፡", "c": "ላሚቷ የሰው ክልል ጣሰች ፡፡", "d": "የተጠየቀችውን እስላሟ ሴት ከለከለች ፡፡", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "የስነቃልን ባለቤት በተመለከተ የትኛው ትክክል ነው?", "a": "የማህበረሰቡ የወል ሃብት ነው፡፡", "b": "ደራሲዎች በጋራ የፈጠሩት ነው፡፡ ", "c": "ታላላቅ አባቶች በስምምነት የፈጠሩት ነው፡፡", "d": "የታሪክ ምሁራን የፈጠሩት ነው፡፡", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "አቶ ደግአረገ ልበሙሉነቴ ጠቀመኝ ቢሉ፣የተሰመረበት ቃልአገባባዊ ፍችው ምንድን ነው?", "a": "ደፋርነቴ", "b": "ሚስጢር ጠባቂነቴ", "c": "ጀግንነቴ", "d": "ትዕግስተኛነቴ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "አሁን ምን ያደርጋል ነገር መለቃቀም፣\nባባቷ ያልሆነ ባያት ምን ልጠቀም፡፡የዚህ ቅኔ ህብረቃል የቱ ነው?", "a": "ባያት", "b": "ምን ልጠቀም", "c": "ባባቷ", "d": "መለቃቀም", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "በአንድ ዓረፍተነገር ውስጥ የዓረፍተነገሩ ባለቤት የሚገኝበት የሐረግ ዓይነት ምን ይባላል;", "a": "ስማዊ ሐረግ", "b": "ቅጽላዊ ሐረግ", "c": "ግሳዊ ሐረግ", "d": "ግሳዊ ሐረግ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ልብ ወለድ በሚጻፍበት ጊዜ ታሪኩ የሚያወራው ስለማን ነው ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው መልስ የትኛውን የልብወለድ አላባ ይመለከታል፡፡", "a": "ገጸባህሪያትን", "b": "መቼትን", "c": "አንጻርን", "d": "ታሪክን", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "የቋንቋ ክሂሎች በቅደምተከተል ሲቀመጡ ከሚከተሉት የትኛው ትክክል ነው?", "a": "ማዳመጥ፣መጻፍ፣መናገር፣ማንበብ ", "b": "መናገር ፣ማዳመጥ፣መጻፍ፣ማንበብ", "c": "ማዳመጥ፣መናገር፣ማንበብ፣መጻፍ", "d": "ማዳመጥ፣መጻፍ፣መናገር፣ማንበብ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "‹‹ደንቆሮ›› የሚለው ቃል በጥቅስ ምልክት የተቀመጠበት ምክንያት ምንድን ነው?", "a": "ሟቹ የአዋቂ አጥፊ ስለሆነ", "b": "የሟቹ ንግግር ስለሆነ", "c": "የተራኪው ንግግር ስለሆነ", "d": "አባባል ስለሆነ", "answerKey": "a", "context": "ግጥም:\n\nየሞተው ወዳጄ እኔ የማልናፍቀው፣\nያነሳኛል አሉ ሲጨንቀው ሲጠበው፣\nመቆያው ማደሪያው ከቤቴ ከደጄ\nምንድን ይሻ ይሆን ትልቁ ወዳጄ?\nታዲያ ምን ይሉታል እንዲህ ያለውን\nከመቃብር በታች ነፍስ የዘራውን፡፡\nምናልባት ሲቀበር ዐፈር አልባሾቹ፣\nኮረትና ድንጋይ አልጫኑት ከታቹ፡፡\nነፍስ እንዳለው ፍጡር እንዳልተቀበረ፣\nምነዋ ወዳጄ ብዙ ቀባጠረ?\nመኖርም መሞትም አንዴ ጥርስን ነክሶ፣\nወይ በምግባር ከብሮ ወይ በምግባር ረክሶ፣\nእንጅ እንደ ወዳጄ መች መቃብር ምሶ፣\nእንጅ እንደ ወዳጄ መች ለራስ አልቅሶ፣\nየቁም ሞትን ሙቶ በተንኮል ጨንብሶ፣\nካልሆነ በስተቀር የ‹‹ደንቆሮ››ለቅሶ፣\nመልሶ መልሶ መልሶ መላልሶ፡፡", "grade": 10, "preamble": "ቀጥሎ የቀረበውን ግጥም መሰረት አድርጋችሁ ለሚከተለው ጥያቄ ከተሰጡት አማራጮች መካከል ትክክለኛውን መልስ የያዘውን ፊደል ምረጡ፡፡", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "በፊደል ‹‹ፀ ›› ___ የሚል ቃል ይመሰረታል፡፡", "a": "ፀሀይ", "b": "ዐይን", "c": "ወርቅ", "d": "", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 1, "preamble": "", "category": "Grammar" }, { "question": "ስሚ አንቺ እማማ ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆች የታፈርሽ ነሽ እኮ ፡፡ \n\nብንል በየትኛው የዘይቤ ዓይነት ተጻፈ፡፡", "a": "እንቶኔ", "b": "ሰውኛ", "c": "ተምሳሌት", "d": "ተለዋጭ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "በስነቃል ክዋኔ ጊዜ የተደራስያን ተግባር ያልሆነው የቱ ነው?", "a": "ስነቃሉን መምራት", "b": "ማዳመጥ", "c": "የሚከውነውን አካል ማጀብ", "d": "ምላሽ መስጠት", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ተረበኛ ለሚለው ቃል ሊመሳሳለው የሚችለው የትኛው ነው?", "a": "ቀልደኛ", "b": "ወገኛ", "c": "ጉረኛ", "d": "መተተኛ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ከሚከተሉት አማራጮች መካከል ስማዊ ሐረግ የሆነው የትኛው ነው?", "a": "ትናንት ያየኋት ቀይ መኪና", "b": "ከወንድሙ ጋር", "c": "እንደ እህቷ በጣም ቀልጣፋ", "d": "ትህትናዋ የሚማርከው አስተናጋጅ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "በተራ ቁጥር‹‹ 12›› የተጠቀሰው ስህተት ዓይነት ምንድን ነው?", "a": "የቁጥር ", "b": "የተሳቢ", "c": "የመደብ ", "d": "የቃላት ምርጫ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ቀጥሎ ከተዘረዘሩት ቃላት መካከል ቅጽል የሆነው ቃል የትኛው ነው?", "a": "ትኩስ", "b": "እሸት", "c": "ድንገት", "d": "ዛሬ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ለጤንነት የበለጠ ጠቀሜታ ያለው አትክልት ወይስ ስጋ ? የሚለው ዓረፍተነገር ለየትኛው የድርሰት ዓይነት ምሳሌ ሊሆን ይችላል?", "a": "ለአመዛዛኝ", "b": "ለገላጭ", "c": "ለተራኪ", "d": "ለስዕላዊ", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ሰው በተፈጥሮው እንዲፈጸምለት የሚፈልጋቸው ነገሮች ምንድን ናቸው?", "a": "ሁሉም", "b": "የረሃብ ፍላጎቱ", "c": "የመበቀል ፍላጎቱ", "d": "ነጻ የመሆን ፍላጎቱ", "answerKey": "a", "context": "ምንባብ:\nሰው በተፈጥሮው የረሃብና የጥም ፣የበቀልና የመሳሰለው ፍልጎቱ ሁሉ እንዲፈጸምለት ይፈልጋል፤ነገርግን ማህበሩ እያንዳንዱ ሰው የተፈጥሮ ፍላጎቱን ለመፈጸም ሲል ሌሎቹን ሰዎች እንዳይጎዳ የሚወስንበት የጽህፈትና የልማድ ሕግ ሠራ፡፡ስለዚህ የተፈጥሮ ፍልጎቱን ለመፈጸም የማህበበሩን የጽህፈትና የልማድ ሕግ የተላለፈ ነውረኛ ተብሎ ይፈረድበታል፡፡\nአንድ ሰው ከሌላው የሚያስቆጣ ነገር ቢደርስበትና ለቁጣው ምክንያት የሆነውን ሰው ለማጥፋት ቢወድ፣ በማህበሩ ህግ ቅጣት እንደሚያስከትል ስለሚያውቅ ቁጣውን ለማብረድ ፣ሌላ የሚበቀልበት አማራጭ መንገድ መመፈለግ አለበት፡፡ስለዚህ የሰው ሰውነት የነጻነትና የጭቆና ውጤት ነው ማለት ይቻላል፡፡ይህ ነጻነትና ጭቆና ማህበሩ በረጅም ዘመን ዕድሜው ከልማዱ፣ከወጉ፣ከህጉ አዋህዶና አስማምቶ የሰራው ነው፡፡ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው ተወልዶ ውስጡ ሲገባ በሱ ተመርቶ መኖር አለበት፤ከማህበሩ ስርዓት አንድ ነቁጥ እንኳን አይተላለፍም፡፡\nበጠቅላላው የማህበር ትምህርት እያንዳንዱ ሰው ሲወለድ ይዟቸው የሚወለደውን ጠቃሚ ውጥኖች ነጻነት በመስጠትና በልዩልዩ መንገድ በመርዳት ጎጂዎቹነንም እንዲሁ በልዩልዩ መንገድ በመጠቆምና በማረም ሰውዬውን ማህበራዊ እንዲሆን ያደርገዋል", "grade": 10, "preamble": "ከዚህ በታች የቀረበውን ምንባብ መሰረት አድርጋችሁ ለሚከተለው ጥያቄ ከተሰጡት አማራጮች መካከል ትክክለኛውን መልስ ምረጡ፡፡", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ፊደል ‹‹ሰ ›› እና ፊደል ‹‹ሠ ›› ___ ፊደላት ናቸው፡፡", "a": "ሞክሼ", "b": "መንታ", "c": "ዘመድ", "d": "", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 1, "preamble": "", "category": "Grammar" }, { "question": "የአንቀጽ ቅርጽ የሚወሰነው በምን መነሻነት ነው?", "a": "ኃይለቃሉ በሚገኝበት ስፍራ", "b": "አንቀጹ በሸፈነው ሃሳብ", "c": "በአንቀጹ መዘርዝር ዓረፍተነገሮች አማካኝነት", "d": "በዓረፍተነገሮች ብዛት", "answerKey": "a", "context": "", "grade": 10, "preamble": "", "category": "Reading comprehension" }, { "question": "ተራኪው ስለ ሟቹ ስላለው አመለካከት ምን ማለት ይቻላል?", "a": "እንደማይወደው መናገር ይቻላል፡፡", "b": "እንደሚወደው መናገር ይቻላል፡፡", "c": "እንደማያውቀው መናገር ይቻላል፡፡", "d": "እንደረሳው መናገር ይቻላል፡፡", "answerKey": "a", "context": "ግጥም:\n\nየሞተው ወዳጄ እኔ የማልናፍቀው፣\nያነሳኛል አሉ ሲጨንቀው ሲጠበው፣\nመቆያው ማደሪያው ከቤቴ ከደጄ\nምንድን ይሻ ይሆን ትልቁ ወዳጄ?\nታዲያ ምን ይሉታል እንዲህ ያለውን\nከመቃብር በታች ነፍስ የዘራውን፡፡\nምናልባት ሲቀበር ዐፈር አልባሾቹ፣\nኮረትና ድንጋይ አልጫኑት ከታቹ፡፡\nነፍስ እንዳለው ፍጡር እንዳልተቀበረ፣\nምነዋ ወዳጄ ብዙ ቀባጠረ?\nመኖርም መሞትም አንዴ ጥርስን ነክሶ፣\nወይ በምግባር ከብሮ ወይ በምግባር ረክሶ፣\nእንጅ እንደ ወዳጄ መች መቃብር ምሶ፣\nእንጅ እንደ ወዳጄ መች ለራስ አልቅሶ፣\nየቁም ሞትን ሙቶ በተንኮል ጨንብሶ፣\nካልሆነ በስተቀር የ‹‹ደንቆሮ››ለቅሶ፣\nመልሶ መልሶ መልሶ መላልሶ፡፡", "grade": 10, "preamble": "ቀጥሎ የቀረበውን ግጥም መሰረት አድርጋችሁ ለሚከተለው ጥያቄ ከተሰጡት አማራጮች መካከል ትክክለኛውን መልስ የያዘውን ፊደል ምረጡ፡፡", "category": "Reading comprehension" } ]